Thursday, May 8, 2014

የሃሮማያ ዩንቨርስቲ ፕሬዚዳንት ታስርው እየተመረመሩ ነው።

የሃሮማያ ዩንቨርስቲ ፕሬዚዳንት ታስርው እየተመረመሩ ነው።
ወርቅነህ ገበየሁ ሃሮማያ ናቸው።
በሀሮማያ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች ማደርያ ፍለጋ በሀረር ከተማ እየተቅበዘበዙ ነው፡፡
ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ መንግስት ሀላፊነት ወስዶ ሊያስተምር የተቀበላቸውን የ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እየጨፈጨፈ ነው። 300 ተማሪዎች ስላሴ ቤተክርስትያን የተጠለሉ ሲሆን በብአዴን ካድሬዎች ቤተክርስትያኑን ለቀዉ ወደዶርም እንዲገቡ ቢነገራቸውም ተማሪዎች ግን ወደ ጊቢ ገብተን እንደገና ላለመደብደባችን ምን ዋስትና አለን በማለት ላይ ናቸው፡፡
በተጨማሪም የዩኒቨርስቲው አስተዳደር ለቤተክርስቲያኒቱ ተማሪዎችን ከግቢዋ እንድታሶጣ ደብባቤ እንደጻፈ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በተጨማሪም በትላንትናው እለት ትራንስፖርት ሚኒስተሩ አቶ ወርቅነህ ገበየው ሓሮማያ ዋናው ጊቢ የመጡ ሲሆን ተማሪው ትምህርት እንዲጅምር እያግባቡ ቢሆንመ በግቢው ውስጥ ሲማሩ ከነበሩት 12500 ተማሪዎች ውስጥ በ አሁን ሰአት ያሉት 3000 ተማሪዎች መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ብዛታቸውም የተገኘው የተማሪዎች መመገቢያ እየመጡ የሚመገቡት እነዚህ ብቻ በመሆናቸው እንደሆነ ታውቃል፡፡
በዛሬው እለት ግን ቁርስ ለመመገብ የመጡት ተማሪዎች 1900 ብቻ ናቸው፡፡ ይህ በእንዲሀ እንዳለ ዩኒቨርስቲው ውስት የመንግስተ ሹመኞች ተደጋጋሚ ስብሰባ ያደረጉ ሲሆን ከምክትል ፕሬዜዳንት ፕ/ር ጨመዳ ፊንሳ በቀር ዋናው ፕሬዜዳንት ሰሞኑን እንዳልታዩ ለማወቅ ተችላል፡፡ አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ዋናው ፕሬዜዳንት ታስሮ እየተመረመረ ነው፡፡ ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

No comments:

Post a Comment