በደብረብርሃን ወያኔ ሞባይል ፍተሻ ላይ ተሰማርቷል። #Ethiopia #DebreBirhan
"መጀመሪያ የሚፈተሸው የተጠቀምከው ድህረገጽ ነው።" ነዋሪዎች
በሰሜን ሸዋ ደብረብርሃን የወያኔ የደህንነት ሃይሎች የነዋሪዎችን ሞባይል በመፈተሽ እንዲሁም የሞባይል ጠጋኞችን በማስገደድ ሊሰሩ የመጡ ሞባይሎችን ከተጠገኑ በኋላ ባለቤቶቻቸው እጅ ሳይደርሱ ከነሚሞሪው በመፈተሽ እና እንዲሁም የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በመለየት በቀጥታ በየጊዜው የሚፈትሹት የተጠቀሟቸውን ድህረገጾች እና የማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴዎቻቸውን መሆኑ ታውቋል።
በሰሜን ሸዋ ደብረብርሃን የወያኔ የደህንነት ሃይሎች የነዋሪዎችን ሞባይል በመፈተሽ እንዲሁም የሞባይል ጠጋኞችን በማስገደድ ሊሰሩ የመጡ ሞባይሎችን ከተጠገኑ በኋላ ባለቤቶቻቸው እጅ ሳይደርሱ ከነሚሞሪው በመፈተሽ እና እንዲሁም የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በመለየት በቀጥታ በየጊዜው የሚፈትሹት የተጠቀሟቸውን ድህረገጾች እና የማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴዎቻቸውን መሆኑ ታውቋል።
የሞባይል ጠጋኞቹ እንደሚሉት ንብረቶቻቸው እና ሙዚቃ የሚጭኑባቸው ኮምፒዩተሮች ሳይቀሩ የተወሰዱ መሆን በመናገር ለጸጥታ ሃይሎች ለመተባበር ፍቃደኛ ካልሆኑ ንብረቶቻቸው እንደማይመለሱ እና እንዲሁም ከዛሬ ነገ እንታሰርለን በሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዲገቡ የደህንነት ሃይሎቹ ሽብር እየፈጠሩ መሆኑን ከስፍራው የመጣ መረጃ ያመለክታል።
የገንዘብ ጥማት ያለባቸውን ፖሊሶች በማስከተል ከግንቦት የመጀመሪያ ሳምንት ጀምሮ አፈሳ ፍተሻ እና ወከባ የሚያካሂዱት የደህንነት ሃይሎች የሞባይል ጥጋኞችን እና ሙዚቃ በመጫን የሚተዳደሩትን ኮምፒዩተሮቻቸውን በመውሰድ ....ኮምፒዩተሩ ባዶ ሆኖ ቢገኝ እንኳን በሪከቨሪ ሶፍትዌር በባለሙያዎች ተደጋጋሚ ምርመራ እየተደረገ ዜጎችን በማንገላታት በማሰር ፍርድ ቤት ድረስ በማቅረብ 2000 ብር ዋስሰንDኢጠሩ ያስደረጉ ቢሆንም ፍርድ ቤት የሚሰሩት ስራ ህጋዊ ስለሆነ አያስከሥም በማለት በነጻ ቢያሰናብትም የደህንነት ሃይሎቹ እያሰሩ በመፍታት ከህግ በላይ እያሰቃይዋቸው መሆኑን አክለው ገልጸዋል።