Friday, February 28, 2014

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና …

 
ealines
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሎሜ፣ማላዊ እና ቶጎ በመሳሰሉ የአፍሪካ አገሮች ከፍተኛ አክሲዮን ሼር በመግዛት እያስተዳደረ እና እያንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ እንዲሁም የተለያዩ የአፍሪካ አገር ተወላጆች በአብራሪነት እና በቲክኒሻንነት እያሰለጠነ ይገኛል፡፡ ይህ ደገሞ አየር መንገዱ በበለጠ በአፍሪካ እና በተቀሩት የዓላም አገራት ተቀባይነት ለማግኘት የሚያስችሉት መልካም ተግባራቶች ናቸው፡፡ እንዲ አይነቱ ለውጥ እና እድገት ለአገር ኩራት ስለመሆኑ ጥርጣሪ የሚያሳድር አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ ከላይ የተገለፁት የአየር መንገዳችን መልካም ስራዎች በተቋሙ ውስጥ ለሚታዩ የአስተዳደር ችግሮች እና አየር መንገዱ ሊደርስበት ይገባው ለነበረ የእድገት ደረጃ አለመድረስ ምክንያቱ ምን እንደሆነ እና መሰል አሳቦችን አንስቶ ለመወያየት ብልጭ ድርግም የሚለው የአየር መንገዳችን እድገት የአሳብ ፍጭት ለማድረግ የሚገድብ አይደለም፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የራሱ የሆነ ድንቅ ታሪክ ያለው ነው፡፡ የአየር ኃይል ካፒቴኖቻችን እንደ ንስር አሞራ ከሰማይ ወደ ምድር በሚገርም ብቃት በመብረር ጠላትን እና የጠላት ሠፈርን አመድ በማድረግ የሚታወቁ ናቸው፡፡ እንዲህ አይነቱ ግርማ ሞገስ ያለው የአገር ኩራት የሆነው ተቋም እና ተቋሙ ያፈራቸው ባለሙያዎች በወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ቀጥተኛ ትዕዛዝ ለመፍረስ በቃ እንጂ፡፡ ተቋማትን አፍርሶ እንደ አዲስ መገንባት አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የስርዓቱ ዋንኛ መገለጫ ነው፡፡ ለዚህም ነው ሁሉ ነገር እንደአዲስ የመጀመር መርዘማ የሆነ የኋላ ጉዞ ሙጥኝ ብለው የተያያዙት፡፡ የሰዎቹ አደገኝነት የሚጀምረው ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንደ አገር መታየት ከጀመረች መቶ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ነው ብለው የነገሩን ዕለት ነው፡፡ በዚህም መሠረት የኢትዮጵያን አየር ኃይል በማፍረስ አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በአዲስ መልክ እንዲቋቋም ያደረገ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት እጅግ በጣም ድንቅ የሆኑ የአየር ኃይል ካፒቴኖቻችን ከአገር ለመሰደድ ተገደዋል፡፡
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት የአንድ ሳንቲም ግልባጭ የሆኑት የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አየር ኃይል ካፒቴኖቻችን ሽሽትና ምክንያት እንዲሁም ውጤት በአጭሩ ለማየት ከላይ የቀረበው አሳብ እንደመንደርደሪያን ሊያገለግል ይችላል፡፡
በአብዛኛው የአየር መንገድ ሠራተኞች በተለይ በአብራሪዎች እና በቴክኒሻኖች የሚነሳው ጥያቄ አስተዳደራዊ በደሎች ናቸው፡፡ እነዘህም ተመጣጣኝ የደሞዝ ክፍያ፣የሰራ እድገት እና የስራ ዝውውርን የሚመለከት ነው፡፡ ለምሳሌ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የሚሰራ ኢትዮጵያዊ አብራሪ የወር ደሞዙ ትልቁ 7 ሺህ ዶላር ሲሆን ( ይህ የገቢ ግብር ጭምር የሚያካትት ነው) ለውጭ አገራት ዜጎች ግን ላቅ እንደሚል ሠራተኞች ይናገራሉ፡፡ በእርግጥ በኢትዮጵያ የኑሮ ሁኔታ ሲታይ የብሩ መጠን ከፍተኛ ነው፡፡ ነገር ግን ክፍያው የሚፈፀመው የኢትዮጵያ አየር መንገዱ አለም አቀፍ እንደመሆኑ መጠን አለም አቀፍ ደረጃ በጠበቀ መልኩ ነው መሆን ያለበት፤ ለዚህም ነው ወራዊ ደሞዝ በብር ሳይሆን በዶላር የሚከፈለው፡፡ ይህንን መሠረት በማድረግ ነው የአየር መንገድ ካፒቴኖች ለስራቸው ተመጣጣኝ ክፍያ እንዲከፈላቸው የሚጠይቁት፡፡
ይሁን እንጂ ሠራተኞች እንደሚናገሩት አስተዳደሩ ለጥያቂያቸው ተገቢ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ‹‹ስራውን መልቀቅ ትችላላችሁ›› ነው የሚባሉት፡፡ በዚህም ምክንያት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ዋና እና ምክትል አብራሪዎች ከአገር በመውጣት በተለያየ አገር የሥራ ብቃታቸውን እያሳዩ ይገኛሉ፡፡ ነገሩን የበለጠ ግልፅ ለማድረግ እንዲረዳ ይህን መመልከት በቂ ይመስለኛል ባለፈው ሳምንት ተጠለፈ የተባለው ኤጥ 702 አውሮፕላን ዋና አብራሪ የነበሩት ግለሰብ ኣኢር እታሊአ (ኣል-እታኢአ) በተባለ የአየር መንገድ ድርጅት ውስጥ ሲያገለግሉ ቆይተው በውር 3 ሺህ ዶላር እየተከፈላቸው በጡረታ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እኚህ ግለሰብ በኢትዮጵያ አየር መንግድ ውስጥ 14 ሺህ ዶላር እየተከፈላቸው ይገኛል ፡፡
ሌላው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አገራት ውስጥ ሎሜ፣ ቶጎ እና ማላዊ እንዲሁም በተቀሩት ማህከላዊ ምዕራብ አፍሪካ አገራት ውስጥ ባለው ከፍተኛ የሼር መጠን የሚያንቀሳቅሳቸው እና የሚያስተዳድራቸው የአየር መንገድ ድርጅቶች አሉ፡፡ በእነዚህ የአየር መንገድ ድርጅቶች ውስጥ በቴክኒሻንነት የሚያገለግሉ ማንኛው የውጪ አገር ዜጋ ከ 3 እስከ 5 ሺህ ዶላር ክፍያ ያገኛል፡፡ ነገር ግን ተመሳሳይ የት/ት እና የስራ ልምድ ያለው ኢትዮጵያዊ ቴክኒሻን የሚከፈለው 1 ሺህ ዶላር የማይሞላ ነው፡፡
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርጅት ውስጥ ሌላው በሠራተኞች ዘንድ ትልቅ ቅሬታ ሆኖ የሚነሳው የስራ ዝውውር እና እድገት ግልፅነት እና ተጠያቂነት የሌለው መሆኑ ነው፡፡ወደ ተሻለ የስራ ቦታ ለመዘዋወር እና የደረጃ እድገት ለማግኘት በአብዛኛው በቅርብ አለቃ መላካም ፍቃድ ላይ የተመሰረተ እንጂ የሥራ ውጤትን ግብ ያደረገ አይደለም፡፡ ይህም ማለት በአየር መንገድ ድርጅት ውስጥ በሚኖሩ የስራ ክፍሎች በዋና ተጠሪነት የሚቀመጡት በአብዛኛው ለወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ቅርብ ከመሆናቸው በላይ ለስርአቱ ደም እና አጥንታቸውን የገበሩ ናቸው፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ ለሰራተኛ እድገት እና ዝውውር ዋንኛ መመዘኛ በማድረግ ተመልክተው ፍቃዳቸውን የሚሰጡት የሰራተኛው የስራ ልምድ እና የት/ት ዝግጅት በመመልከት ሳይሆን፣ ለወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ያለውን አመለካከት እና ጎሳን መሠረት ያደረገ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ አብዛኛው የአየር መንገድ ሰራተኞች በድርጅታቸው ለሚታየው የአስተዳደር ችግሮች በቁጭት ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ የተቀሩት ደግሞ ሰራቸውን በመልቀቅ ከአገር ወጥተው ይገኛሉ፡፡
ይህ በእንዲ እንዳለ ከሰሞኑ ትልቅ አጀንዳ በመሆን መነጋገሪያ የሆነው የረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራ የአውሮፕላን ጠለፋ ነው፡፡ የአውሮፕላን ጠለፋ ፖለቲካን መሰረት አድርጎ በአገራችን የተጀመረው ህዳር 29 ቀን 1965 ዓ.ም ሲሆን እነዋለልኝ መኮንን እና ማርታ መብራቱ ያካተተ ነበር፡፡የያኔው ጠላፋ ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ዋና አሳቡ ፖለቲካ ጥገኝነትን በመጠየቅ ከአገር ሸሽቱ ለመኖር ሳይሆን በጃንሆይ እና በአስተዳደራቸው ላይ ለተነሳው አመፅ የአውሮፕላን ጠለፋው የአመፁ የእስትራቴጂ አካል ጭምር ስለነበረ ነው፡፡
በእንዲ መልኩ የተጀመረው ፖለቲካዊ ይዘት ያለው የአውሮፕላን ጠለፋ በደርግ መንግስት ምን ያህል ተግባራዊ እንደሆን መረጃ ለማግኘት በእኔ በኩል ያልተቻለኝ ቢሆንም፤ ነገር ግን የአውሮፕላን ጠለፋ በቁጥር እና በአይነት በዝቶ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ጠለፋ የታየው በወያኔ/ኢህአዴግ የመንግስት የአስተዳደር ወቀት ስለመሆኑ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ እንዲሁም ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ የመንገደኛ እና የጦር አውሮፕላን ካፒቴኖች በተለያየ አገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው  በመኖር ላይ ይገኛሉ፡፡
በእርግጥ የእነዚህ ካፒቴኖች የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቅ በራሱ የእውነት ፖለቲካዊ ይዘት አለው ወይስ የለውም ለማለት ተገቢ የሆነ ጥናትና እውነታን የሚጠይቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ካፒቴን ተሾመ ተንኮሉ እና መስል አጋሮቹ በመንግስት ከደረሰባቸውን በደልና ግፍ በላይ በአገር ላይ የሚፈፀም በደል አላስችል ሲላቸው የፈፀሙት ገድል ሁሌም ታሪክ በበጎ የሚያስታውሰው ነው፡፡
ሌላው እና ለዚህ ጹሑፍ ዋንኛ መነሻ የሆነው አሳብ የረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራ ጉዳይ ነው፡፡ እኔ ብቻ ሳልሆን ማንም ሰው በእርግጠኝነት ሊናገር የሚችለው አውሮፕላኑ ከአዲስ አበባ መነሳቱ እና ጄኔቫ ማረፉ ሲሆን፣ አውሮፕላኑ በጄኔቫ ያረፈው በታቀደው መልኩ ሳይሆን ከዚያ ውጪ በሆነ በረዳት አብራሪ ሃይለመድን አበራ ፍቃድ ብቻ መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ያሉ ነገሮች በአብዛኛው መላ ቅጡ በጠፋ መረጃ የተተበተበ ነው፡፡ በማህበራዊ ድረ-ገፅ እና በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች የሚነገሩ ነገሮች በአብዛኛው የወያኔ/ኢህአዴግ  መንግስት ደጋፊ፣ እንዲሁም ተቃዋሚም የሆን ሁሉ ዋንኛ መነሻ አሳባብ ከራስ ጥቅም እና ፍላጎት የመነጨ ነው፡፡ ይህም ስለመሆኑ የተነገሩት እና የተለቀቁትን መረጃዎች በማየት መገንዘብ ይቻላል፡፡
የነገሩን ውስብስብነት የበለጥ የሚያገላው ደግሞ የፓይለቱ ቤተሰቦች የሚሰጡት መረጃ ነው፡፡ ለማሳየነትም እንዲረዳ እህቱ ፣አክስቱ ፣ወንድሙ እንዲሁም የአጎቱ ባለቤት እና የቅርብ ጎደኛ በጉዳዩ ላይ የሚሰጡት ቃላቸው ፈፅሞ ሊቀራረብ የማይችል ነው፡፡ በተለይ ታላቅ ወንድሙ በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ባደረገው ቃለ መጠይቅ በአብዛኞቻቸን ዘንድ ሞቅ አድርግን ይሆናል ብለን በገመትነው ነገር ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ነው የደፋበት፡፡
ይድነቃቸው ከበደ
ይድነቃቸው ከበደ
የረዳት ካፒቴን ሃይለመድን አበራ አውሮፕላኑን የጠለፈበት ምክንያት በእርግጠኝነት ልናውቅ የምንችለው ከራሱ በሚነገር እውነት ብቻ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ቀኑ የራቀ አይደለም ፤ስለዚህም ቀኑ ተጠብቁ ሙገሳውም ትችቱም ቢቀርብ ይበለጥ የተሻለ ይሆናል፡፡ እኔ በበኩሌ በዚህ ጉዳዩ ከመጀመሪያው ጀምሮ የያዝኩት አቋም ይህን ነው፡፡
የዚህ ጹሑፍ ማጠቃለያ የሚሆነው በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚታዩ ችግሮች ዋንኛ ምክንያት የአስተዳደር የአቅም ውስንነት መሆኑ ነው፡፡ ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ቀጥተኛ የሆነ የመንግስት ጣልቃ ገብነት እና ብልሹ ፖለቲካዊ የአገር አስተዳደር ነው፡፡ በመሆኑም ሥራቸውን ብቻ በማየት በሥራቸው ለደረሰባቸው በደል አየር መንገዱን ለቀው ጥገኝነት የጠየቁ፡፡ እንዲሁም ከሚከፈላቸው ዶላር በላይ ስለአገራቸው እና ስለ ህዝብ ተቆርቁረው እንቢ ለሀገሬ ብለው ለተሰደዱ ለሁሉም ተጠያቂው በስልጣን ላይ ያለው የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ነው፡፡

Golgul

Wednesday, February 26, 2014

በአባይ ግድብ ጉዳይ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር እየተነጋገርኩ ነው አለች

ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 18/2006 (ቢቢኤን) ፦አራት ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ይፈጃል የተባለዉ ግድብን እንገነባለን በማለት የኢትዮጵያ መንግስት በቦንድ ስም ገንዘብ ለመሰብሰብ ያደረገዉ ሙከራ እምብዛም አለመሳካቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ መንግስት የግንባታዉ ፕሮጀክት ሰላሳ አራት ከመቶ ተጠናቋል ቢልም ግብጽ ባሰማችዉ ተቃዉሞ የግድቡ ግንባታ መስተጓጎሉን የመገናኛ ብዙሗን ዘግበዋል።
ABAY
የኢትዮጵያ ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሆኑት አቶ አለማየሁ ተገኑ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ “ኢትዮጵያ ችግሩን ለመቅረፍ ከሱዳን ጋር ዉይይት ጀምራለች” ሲሉ ገለጸዋል። ግብጽን ወደ ዉይይቱ ሒደት ለማምጣት እየተጣረ መሆኑን የገለጹት ሚኒስቴር ሒደቱ ምን እንደሚመስል ግን ያመላከቱት ነገር የለም።
ሱዳንና ግብጽ ከግድቡ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ኢትዮጵያ ብትገልጽም፤ ሁለቱ አገራት ግን ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ ሲሰጡ አልተስተዋልም። ግብጽ ሰማኒያ ከመቶ የሚሆነዉ የዉሃ ሐብቷ ከአባይ እንደሚመጣ ይታወቃል፤ የአባይን ጉዳይ እንደ ህልዉና ስለምትመለከትዉ የህዝብ ድጋፍ የሌለዉ የመላኒየሙ ግድብ እንደምን ዉጤታማ ይሆናል የሚለዉ ጉዳይም አጠያያቂ እየሆነ ነዉ።
ግድቡን ለመገንባት እስከ ሐያ ሺ የሚደርሱ ኢትዮጵያዉያን መፈናቀላቸው የታወቀ ሲሆን 70 ሚሊዮን ኩቢክ ሜትር ዉሃን ያከማቻል ተብሎ የተነገረት ግድብ ከፈነዳ ከፍተኛ የዉሃ መጥለቅለቅ ሊፈጥር ይችላል የሚል ስጋት አለ።
ኢትዮጵያ ግድቡ በአዉሮፒያኑ ቀመር 2017 ሲጠናቀቅ እስከ ስድስት ሺ ሜጋ ዋት የሚደርስ የኤለክትሪክ ሐይልን ለማመንጨት ብቃት ይኖረዋል ትላለች። ይህ ዉጥን ከግድቡ ባላንጣዎች ከሱዳናን ግብጽ ብቻ ሳይሆን” አባይ ከመገደቡ በፊት የመብት ጥሰቱ ይከበር” ከሚሉ ኢትዮጵያዉያንም ጭምር ጽኑ ተቃዉሞ እየገጠመዉ ነዉ። ኢትዮጵያ ከፕሮጀክቱ ዋነኛ ባላንጣ ከግብጽ ጋር በቀጥታ መነጋገር ሲገባት፤ ከሱዳን ጋር ዉይይት መጀመሯ ለምን እንደሆነ የዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴሩ ግልጽ አላደረጉም።
ABAY 2
በተያያዘ ዜናም ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማሪያም ደሳለኝ ቀደም ሲል በህዳር 24/2006 ወደ ሱዳን ተጉዘዉ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸዉንና ህወሃት የተመሰረተበትን 39ኛ አመት ለማክበር የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኡመር ሐስን አልበሽር በየካቲት 11/2006 ወደ መቐሌ መጓዛቸዉን ይታወቃል።ይህ ከወትሮ የተለየ ቁርኝት እንደምን ተከሰተ በማለት ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖችም አሉ።
የሱዳን የዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አሊ አልቀርዲ በህዳር 23/2006 ኢትዮጵያና ሱዳን ያላቸዉን የድንበር ልዩነት አስወግደዉ መስማማታቸዉን ይፋ አድርገዋል።
ኢትዮጵያ ድንበሯን ለሱዳን ቆርሳ ለመስጠት መስማማቷ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያለዉ ብቻ ሳይሆን ህወሃት በስልጣን ለመቆየት የተቃዋሚ ሐይላትን ለመግታት አጎራብች አገራትን እየደለለ ነዉ የሚሉም አሉ።ህወሃት ስልጣኑ በህዝብ ከተወሰደ ሐብትን ወደ አጎራባች አገሮች አሽሽቶ ለመደላደል የሚያደርገዉ ሴራ ይኖራል በማለት ጉዳዩን ከመልካዓምድራዊ የፖለቲካ አለመረጋጋት ጋር የሚያይዙም አሉ።
አንድንድ ተንታኞች ደግሞ አባይን መገደብ የሚለዉ ሐሳብ ሶስት ዲሞክራሲያዊ ያልሆኑ አገራት አንባገነናዊ መንግስቶች በስልጣን ላይ ለመቆየት የሚያደርጉት ወከባ ነዉ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በግድቡ ስም ገንዘብ ሲሰበስብ፤ ሱዳንና ግብጽ ደግሞ ብሔራዊ የሆነ ስጋት እንዳንዣበበ በመስበክ ህዝብን የሚያደናግሩበት ትርኢት ነዉ ይላሉ።
ቀድም ሲል ባሶንዳ በሚባለዉ የሱዳን የጠረፍ ከተማና አካባቢ 77 ኢትዮጵያዉያን በሱዳናዉያን መገደላቸዉን ቢቢኤን ዘግቦ ነበር ።ይህ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት እንዳለዉ ባይታወቅም፤ የሚታወቀዉ ነገር ግን የኢትዮጵያ ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሆኑት አቶ አለማየሁ ተገኑ የአባይ ግድብ አስመልክቶ ከሱዳን ጋር ዉይይት መኖሩን መናገራቸዉ ነዉ።
በሱዳን ስለሞቱት 77 ኢትዮጵያዉያን የሚናገር ይኖር ይሆን?የኢትዮጵያ እና የሱዳን መንግስታት ስል ድንበር ስምምነት፣የጋራ ስለሆነ ደህነነትና ጥበቃ፣ህገወጥ የሆነ የሰዎች ዝውዉርን ስለመግታት፣የኤለክትሪክ ሐይልን ስለመጋራት፣የአባይን ግድብን አስመልክቶ ስለሚደረጉ ዉይይቶች ብቻ ነዉ እየገለጹ ያሉት።
Ze-Habesha Website

Tuesday, February 25, 2014

Ethiopia: Land, Water Grabs Devastate Communities

February 20, 2014

Satellite Images Show Devastating Toll on 500,000 Pastoralists

Human Rights Watch
(Nairobi)New satellite imagery shows extensive clearance of land used by indigenous groups to make way for state-run sugar plantations in Ethiopia’s Lower Omo Valley, Human Rights Watch and International Rivers said today. Virtually all of the traditional lands of the 7,000-member Bodi indigenous group have been cleared in the last 15 months, without adequate consultation or compensation. Human Rights Watch has also documented the forced resettlement of some indigenous people in the area.
State-run sugar plantations in Ethiopia’s Lower Omo Valley
LORYRA, SOUTH OMO, ETHIOPIA, DECEMBER 2007: Images of the Dassanech people in the Lower Omo Valley, South West Ethiopia, 14 December 2007. (Photo by Brent Stirton/Getty Images.)
The land clearing is part of a broader Ethiopian government development scheme in the Omo Valley, a United National Educational, Scientific and Cultural Organization (UNESCO) World Heritage Site, including dam construction, sugar plantations, and commercial agriculture. The project will consume the vast majority of the water in the Omo River basin, potentially devastating the livelihoods of the 500,000 indigenous people in Ethiopia and neighboring Kenya who directly or indirectly rely on the Omo’s waters for their livelihoods.
“Ethiopia can develop its land and resources but it shouldn’t run roughshod over the rights of its indigenous communities,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director at Human Rights Watch. “The people who rely on the land for their livelihoods have the right to compensation and the right to reject plans that will completely transform their lives.”
A prerequisite to the government’s development plans for the Lower Omo Valley is the relocation of 150,000 indigenous people who live in the vicinity of the sugar plantations into permanent sedentary villages under the government’s deeply unpopular “villagization” program. Under this program, people are to be moved into sedentary villages and provided with schools, clinics, and other infrastructure. As has been seen in other parts of Ethiopia, these movements are not all voluntary.
Satellite images analyzed by Human Rights Watch show devastating changes to the Lower Omo Valley between November 2010 and January 2013, with large areas originally used for grazing cleared of all vegetation and new roads and irrigation canals crisscrossing the valley. Lands critical for the livelihoods of the agro-pastoralist Bodi and Mursi peoples have been cleared for the sugar plantations. These changes are happening without their consent or compensation, local people told Human Rights Watch. Governments have a duty to consult and cooperate with indigenous people to obtain their free and informed consent prior to the approval of any project affecting their lands or territories and other resources.
The imagery also shows the impact of a rudimentary dam built in July 2012 that diverted the waters of the Omo River into the sugar plantations. Water rapidly built up behind the shoddily built mud structure before breaking it twice. The reservoir created behind the dam forced approximately 200 Bodi families to flee to high ground, leaving behind their crops and their homes.
In a 2012 report Human Rights Watchwarned of the risk to livelihoods and potential for increased conflict and food insecurity if the government continued to clear the land. The report also documented how government security forces used violence and intimidation to make communities in the Lower Omo Valley relocate from their traditional lands, threatening their entire way of life with no compensation or choice of alternative livelihoods.
The development in the Lower Omo Valley depends on the construction upstream of a much larger hydropower dam – the Gibe III, which will regulate river flows to support year-round commercial agriculture.
A new film produced by International Rivers, “A Cascade of Development on the Omo River,” reveals how and why the Gibe III will cause hydrological havoc on both sides of the Kenya-Ethiopia border. Most significantly, the changes in river flow caused by the dam and associated irrigated plantations could cause a huge drop in the water levels of Lake Turkana, the world’s largest desert lake and another UNESCO World Heritage site.
Lake Turkana receives 90 percent of its water from the Omo River and is projected to drop by about two meters during the initial filling of the dam, which is estimated to begin around May 2014. If current plans to create new plantations continue to move forward, the lake could drop as much as 16 to 22 meters. The average depth of the lake is just 31 meters.
The river flow past the Gibe III will be almost completely blocked beginning in 2014. According to government documents, it will take up to three years to fill the reservoir, during which the Omo River’s annual flow could drop by as much as 70 percent. After this initial shock, regular dam operations will further devastate ecosystems and local livelihoods. Changes to the river’s flooding regime will harm agricultural yields, prevent the replenishment of important grazing areas, and reduce fish populations, all critical resources for livelihoods of certain indigenous groups.
The government of Ethiopia should halt development of the sugar plantations and the water offtakes until affected indigenous communities have been properly consulted and give their free, prior, and informed consent to the developments, Human Rights Watch and International Rivers said. The impact of all planned developments in the Omo/Turkana basin on indigenous people’s livelihoods should be assessed through a transparent, independent impact assessment process.
“If Ethiopia continues to bulldoze ahead with these developments, it will devastate the livelihoods of half a million people who depend on the Omo River,” said Lori Pottinger, head of International Rivers’ Ethiopia program. “It doesn’t have to be this way – Ethiopia has options for managing this river more sustainably, and pursuing developments that won’t harm the people who call this watershed home.”
Background
Ethiopia’s Lower Omo Valley is one of the most isolated and underdeveloped areas in East Africa. At least eight different groups call the Omo River Valley home and the livelihood of each of these groups is intimately tied to the Omo River and the surrounding lands. Many of the indigenous people that inhabit the valley are agro-pastoralist, growing crops along the Omo River and grazing cattle.
In 2010, Ethiopia announced plans for the construction of Africa’s tallest dam, the 1,870 megawatt Gibe III dam on the Omo River. Controversy has dogged the Gibe III dam ever since. Of all the major funders who considered the dam, only China’s Industrial and Commercial Bank of China (ICBC) provided financing (the World Bank, African Development Bank, and European Investment Bank all declined to fund it, though the World Bank and African Development Bank have financed related power lines).
The Ethiopian government announced even more ambitious plans for the region in 2011, including the development of at least 245,000 hectares of irrigated state-run sugar plantations. Downstream, the water-intensive sugar plantations, will depend on irrigation canals. Although there have been some independent assessments of the Gibe dam project and its impact on river flow and Lake Turkana, to date the Ethiopian government has not published any environmental or social impact assessments for the sugar plantations and other commercial agricultural developments in the Omo valley.
According to the regional government plan for villagization in Lower Omo, the World Bank-supported Pastoral Community Development Project (PCDP) is funding some of the infrastructure in the new villages. Despite concerns over human rights abuses associated with the villagization program that were communicated to Bank management, in December 2013 the World Bank Board approved funding of the third phase of the PCDP III. PCDP III ostensibly provides much-needed services to pastoral communities throughout Ethiopia, but according to government documents PCDP also pays for infrastructure being used in the sedentary villages that pastoralists are being moved to.
The United States Congress in January included language in the 2014 Appropriations Act that puts conditions on US development assistance in the Lower Omo Valley requiring that there should be consultation with local communities; that the assistance “supports initiatives of local communities to improve their livelihoods”; and that no activities should be supported that directly or indirectly involve forced evictions.
However other donors have not publicly raised concerns about Ethiopia’s Lower Omo development plans. Justine Greening, the British Secretary of State for International Development, in 2012 stated that her Department for International Development (DFID) was not able to “substantiate the human rights concerns” in the Lower Omo Valley despite DFID officials hearing these concerns directly from impacted communities in January 2012.